የአዲስ ጉዞ
የታሪክ ሂደት አዲስ መንገድ

1999-2002
1999-2002

በርናንድ “ቤኒ ዊስለር እና ክርስቲን ኦበርሊ” በጊዜው ጥቅም ላይ የዋሉ ዊልቸሮችን ከስዊዘርላንድ ወደ ኢትዮጵያ በሚያቀርብ የእርዳታ ፕሮጀክት ውስጥ በአዲስ አበባ ከ1999 እስከ 2002 በበጎ ፍቃደኝነት ሰርተዋል፡፡

2003
2003

ክሪስቲን እና ቤኔ ከማሪያን ሎቸር ጋር በመሆን በርን የሚገኘውን የአዲስ ጉዞ ማህበር አግኝተው በአዲስ አበባ የዊልቸር ወርክሾ መስርተዋል፡፡

2003
2003

በጦርነት የተፈናቀሉ ሰዎች በሚገኙበት ማእከል ውስጥ የመሰረት ድንጋይ የመጣል ፕሮግራም ተከናውኗል፡፡ ከጥቂት ወራት በኋላ ከፍተኛ የሆነ የዛገ ብረት ተወግዶ እና ለብዙ ሰአት ብየዳ ከተከናወነ በኋላ ላረጀ ኮንቴነተር የዊልቸር ወርክሾፑ ተገንብቷል፡፡

2004
2004

አዲስ ጉዞ እንደ ውጪ ድርጅት እውቅናን አግኝቷል እና ቢሮ ከፍቷል፡፡

2005
2005

የዊልቸር ባስኬትቦል የስፖርት ሜዳ ተገንብቷል፡፡

2006
2006

የመጀመሪያው የአነስተኛ የስራ እድል ፈጣሪዎች ቡድን ስልጠና ተጀምሯል፡፡

2007
2007

የአካል ጉዳት ላለባቸው ልጆች ወላጆች ማዋያ ተገንብቷል እና የአዋቂዎች ፊዚዮቴራፒ ቀጥሏል፡

2010
2010

በአዲስ የፕሮጀክት ስፍራ ላይ የስራ ፈጣራ ስራዎች ተጀምሯል፡፡ የአዲስ ጉዞ ጊዜያዊ የዳንስ ቡድን ተመሰረተ፡፡

2011
2011

አዲሱ የፕሮጀክት ሳይት የመመረቅ እና የመጀመር ስራ ተከናውኗል፡፡ በዚያው አመት በኢትዮጵያ ውስጥ አካታች የሆነ ሜዳን ለመገንባት ከኩኩክ የባህል ማህበር ጋር አጋር ሆነናል፡፡

2012
2012

ኮሮና! ተገቢ የሆነ መከላከያ በመተግበር ሳናቋርጥ ስራችንን ቀጥለናል፡፡

2013
2013

በተሃድሶ መምሪያችን በልጆች እና በታዳጊዎች ፊዚዮቴራፒ ስፔሻላይዝ አድርገናል እና ቤተሰብን ያማከለ የቅድመ ተደራሽነት ፕሮግራምን አስጀምረናል፡፡

በአጭር አመታት አዲስ ጉዞ ከዊልቸር ወርክሾፕ ተነስቶ ከአካል ጉዳት ጋር ለሚኖሩ ሰዎች የልህቀት ማእከል ወደ መሆን ተሻግሯል፡፡