በ2010 የአዲስ ጉዞ የዳንስ ቡድን ተመሰረተ፣ ወዲያውኑ ዘመናዊ ዳንስን የዳንስ መገለጫችን አድርገን መረጥን፡፡ አካላዊ እና ስሜታዊ መግለጫዎችን ያበረታታል እና በእንቅስቃሴ እና በፈጠራ የግል ነጻነትን ለማግኘት ይረዳል፡፡ ከግል የሰውነት እንቅስቃሴ እና ስብእናቸው የሚመነጭ የተለየ የዳንስ አገላለጾችን ያሳያሉ፡፡
በዚህ አካል ጉዳተኛነታቸውን ይሸፍናል፡፡ አካላዊ ውስንነት መሬት ውስጥ ይቀበራል፡፡ ለብዙዎቹ ተሳታፊዎች ይህ ያልተጠበቀ ልምምድ ነው፡፡ ሁለት የዳንስ ቡድኖች (አስራ ሁለት) ጀማሪዎች እና ሰባት ልምድ ያላቸው ደናሾች በዳንስ ስቱዲዮዋችን ውስጥ በሳምንት ሁለቴ ይለማመዳሉ እና አካል ጉዳተኛ በሆኑ እና ባልሆኑ ልምድ ባላቸው የዳንስ አሰልጣኞች ይሰለጥናሉ፡፡ በዳንስ አቀራረብ ማህበራዊ ግንዛቤ ማስጨበጥ እና ከአካል ጉዳት ጋር ለሚኖሩ ሰዎች እውቅና መስጠትን እናጎለብታለን ብሎም ለረዥም ጊዜ የአካታችነት ጉዞዋችን ወሳኝ የሆነ አስተዋጽኦን ያደርጋል፡፡
አዲስ ጉዞ ስዊዘርላንዳዊ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሲሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ አካል ጉዳተኞች ጋር አብሮ ይሰራል።
Copyright ©2023. Addis Guzo
Design by Negat Creative