ክህሎቶችን
ማሻሻል

የሕይወት ክህሎቶች ለመከላከል፣ ጤናን እና የግል እድገትን ለማጎልበት ወሳኝ የሆነ ሚና ይጫወታሉ፡፡ ሰዎች የእለት ተእለት የሕይወት ጥያቄዎችን እና ተግዳሮቶችን በራሳቸው እና በውጤታማነት እንዲወጡ ያስችላሉ፡፡ ብዙዎቹ የአገለግሎታችን ተጠቃሚዎች በትምህርት እጦት እና ለብዙ አመታት በመገለል ምክንያት የሚጠቅሟቸውን መሰረታዊ የሆኑ ተሞክሮዎች እና መረጃዎችን አጥተዋል፡፡ የክህሎት ስልጠናዎቻችን ከተሃድሶ ፕሮግራም፣ በጠርሙስ ስራ የዕደ-ጥበብ ማእከል ላሉት ሴቶች እና ለስፖርት እና የዳንስ ቡድኑ አባላት የተውጣጡ ቤተሰቦች እና ተንከባካቢዎች ያማከለ ነው፡፡ ሰዎች ራሳቸውን እንዲረዱ ማገዝ በሚለው በዚህ እሳቤ ስር እንደ ጤና ጉዳዮች፣ የጾታ ጉዳዮች፣ የሴቶች ጉዳዮች፣ ጥቃትን መከላከል እና ህጻናትን መንከባከብ የመሳሰሉት ርእሰ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡