የጥቃቅን -ንግድ
ቡድን ለሴቶች

በኢትዮጵያ ውስጥ መንቀሳቀስ ለማይችሉ ሰዎች ትምህርት ለማግኘት፣ ስራ ለመፈለግ ወይም ቢዝነስ ለመምራት በጣም ከባድ ነው፡፡ ላለፉት 8 አመታት በተለያዩ ንግዶች 80 የሚጠጉ ከአካል ጉዳት ጋር የሚኖሩ ሰዎችን አሰልጥነናል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ሁለት ቡድኖች ብቻ የራሳቸውን ንግድ ጀምረዋል፡፡ ከአካል ጉዳት ጋር የሚኖሩ ሰዎች የሕይወት ሁኔታ ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ እና እድገትን ለማስመዝገብ ፈታኝ በመሆኑ ምክንያት መሀከለኛ ስኬት ነው ያስመዘገቡት፡፡ ይህንን ልምድ በመመርኮዝ ከሶስት የተለያዩ የዕደ-ጥበባት ቡድኖች (ከሃያዶል፣ከሰፊ ሲስተርስ እና ከጩጩራ) ለተውጣጡ ለአስራ አንድ ሴቶች ተደራሽ የሆኑ ወርክሾፖቻችንን ማጓጓዣ እና ከስልጠናዎቻቸው በኋላ በሁሉም የስራ ፈጠራ ዘርፎች ምክርን መስጠታችንን ቀጥለናል፡፡ አሻንጉሊት መስራት፣ ልብስ ስፌት እና የጥልፍ (ኪሮሽ) ስራ ለብዙ አመታት በእኛ ዘንድ ስልጠናን ወስደዋል፡፡ ከአዲስ ጉዞ ጥላ ስር የቦትል ብሩሽ ክራፍት ሴንተር ኮፕሬቲቭ ለመመስረት በጋራ ተሰባስበዋል፡፡ በዚህ መንገድ ብቻ ነው ንግዳቸውን በውጤታማነት መምራት እና ቋሚ የሆነ ገቢን ማረጋገጥ የሚችሉት፡፡ ዛሬ ላይ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ምርቶቻቸውን በእጅ የተሰሩ ዕደ-ጥበባት፣ ሱቆች ወይም ባዛሮች በፕሮጀክት ስፍራችን በቀጥታ ይሸጣሉ፡፡ ከእነዚህ ቡድኖች አንደኛዋ አሁን ከአካል ጉዳት ጋር የሚኖሩ ሌሎች ቡድኖችን ታሰለጥናለች፡፡